Featured Article
ወንድነት
የተከታታይ ሳምንታችን የትምህርታችን መጨረሻ ስለነበር ዘግየት ብለን ነበር የወጣቶችን ፕሮግራም የጨረስነው። ውጩም ጨለምለም ማለት ጀምሯልና ጥቂት አብሬያቸው ሳልጫወት ልጆቼ እንዳይተኙብኝ በሚል ወደ ቤት ለመሄድ ጠደፍ ጠደፍ እኔም ማለቴ አልቀረም። በጥድፊያዬ መሀል “ዶ/ር ላንድ ደቂቃ ላናግርህ እችላለሁ አለኝ?” “ሥራ እና ክርስትና” የሚለውን ትምህርታችንን በንቁ ተሳትፎ ሲከታታል የነበረ ወጣት ድምጽ። ላፍታም ሳላመነታ “በደስታ፣” ብዬ ቆም አልኩኝ። ቀጥሎ የተጠየኩት ነገር ያልጠበኩት ነበር።

የጆሮ ያለህ!
ተካልኝ ነጋ (ዶ/ር) በዚህ ጽሑፉ፣ ‘አድማጭ መሆን ለምን ተሳነን? ለምን ተናጋሪ ብቻ ሆንን? በማድመጥ ውስጥ እናገኝ የነበረውን ኁልቁ መሳፍርት በረከትኣ ለምን እናጣለን?’ ሲል አንባቢን ይሞግታል።

ለዋጭ ለውጦች!
አድማጭ የሚሹ ብዙ ጩኸቶች እዚህም እዚያም አሉ። የሰው ልጅ የስኬት ብቻ ሕይወት የለውም፤ ውድቀትም አንዱ የኑሮ ገጽታ ነው። በውድቀት ውስጥ ብዙ ሕመሞች በሰዎች ልብ ውስጥ ተቀርቅረው ይገኛሉ። እነዚህ ሕመሞች እንዲታከሙ የሚያስችሉ አድማጭ ጆሮ ያላቸው መካሪዎች በእጅጉ ያስፈልጉናል ይላል ይህ የተካልኝ ነጋ (ዶ/ር) ጽሑፍ።

አቋራጭ ስሌቶች
“ለጥልቅ አሳቢያን ዐሥርት ዓመታት የወሰዱ ጉዳዮችን፣ በአንድ ቀን የቁም አሰላስሎ ወይም በአንድ ሰው የመጽሐፍ መግቢያ ንባብ የምንደመድም የአቋራጭ መንገድ አፍቃሪያን አለን።” ተካልኝ ነጋ (ዶ/ር)

የመተማመን ድልድዩን እንጠግን
ይቅርታ መጠየቅ ምን ማለት ነው? ሰዎች ይቅርታ ለመጠየቅ ለምን ይቸገራሉ? የተሠራው በደል በተበዳዩ ላይ ካሳድረው ጉዳት አንጻር፣ የበዳዩ ይቅርታ ጥየቃ የሚያጎናጸፈው ሥነ ልቦናዊ ፋይዳ ምንድን ነው?

ያላለቀው ጉዞ!
ተካልኝ ነጋ (ዶ/ር) “ያላለቀው ጉዞ!” ሲል በሰየመው ጽሑፉ፣ በልማትና ዕድገት መካከል ያለውን መሠረታዊ ልዩነት በማስቃኘት፣ አገራችን ኢትዮጵያ “ሄድ መጣ” እያለ የሚያማልላትን ተስፋ በሙሉ እጇ ትጨብጠው ዘንድ ልታደርጋቸው የሚገቡ ያላቸውን አንዳንድ ነጥቦች እንደሚከተለው ያስነብባል።

ዛሬ ያልተመቸን ሕዝቦች
ኢትዮጵያውያን በቀድሞው ዘመን ናፋቂነት የዛሬውን ዕድል እያባከንን እንደ ሆነ፣ ተካልኝ ነጋ (ፒ.ኤች.ዲ) በዚህ መጣጥፉ ይሞግታል። በተለይም በትላንት ናፍቆት ውስጥ ስለ “ጀግኖቻችን” ያለን ምልከታ፣ የዛሬውን አብሮ ነዋሪ ወንድማችንን እንዳይጎዳውም ያሳስበናል።

የሰሞኑ የኅብረቱ ትጭጭት (ጋብቻ)
የአብያተ ክርስቲያናት ኅብረት ቁጥራቸው 150 የሚደርሱ “መንፈሳዊ” ተቋማትን በአጋር አባልነት የመቀበሉን መራር እውነታ አውቀናል። በኅብረቱ መግለጫ ሚዲያ ተጠርቶላቸው የካሜራ ክብር ያገኙት ግን አራቱ ብቻ ናቸው። ሌሎቹ ነገራቸው በድብስብስ የታለፈ ሊባል የሚችል ነው። ራሳቸው በማኅበራዊ ሚዲያ ብቅ ብለው እኛም ነበርንበት ባይሉ መኖራቸውን ከቶውን ባላወቅን ነበር። አራቱ ትኩረት ያገኙበት ምክንያት፣ በተክለ ሰውነት “አውራዎች” ስለሆኑ ይሆናል።


