Resources

Resources2024-11-29T10:23:37+00:00

Featured Article

ወንድነት

የተከታታይ ሳምንታችን የትምህርታችን መጨረሻ ስለነበር ዘግየት ብለን ነበር የወጣቶችን ፕሮግራም የጨረስነው። ውጩም ጨለምለም ማለት ጀምሯልና ጥቂት አብሬያቸው ሳልጫወት ልጆቼ እንዳይተኙብኝ በሚል ወደ ቤት ለመሄድ ጠደፍ ጠደፍ እኔም ማለቴ አልቀረም። በጥድፊያዬ መሀል “ዶ/ር ላንድ ደቂቃ ላናግርህ እችላለሁ አለኝ?” “ሥራ እና ክርስትና” የሚለውን ትምህርታችንን በንቁ ተሳትፎ ሲከታታል የነበረ ወጣት ድምጽ። ላፍታም ሳላመነታ “በደስታ፣” ብዬ ቆም አልኩኝ። ቀጥሎ የተጠየኩት ነገር ያልጠበኩት ነበር።

የተዘነጋው አሁን — Tekalign Nega (Ph.D.) | Hintset

ሁላችን በሐሳብ ባህር ላይ ቀዛፊዎች ነን። ቀዘፋው ደግሞ በትላንት እና በነገ የሐሳብ ማዕበል የሚናጥ ነው። ከትላንት ለመማርም ሆነ ነገን የተሳካ ለማድረግ አሁንን መኖር መጀመር እንዳለብን ይህ የተካልኝ ነጋ (ዶ/ር) መጣጥፍ መንገድ ይጠቁማል።

የጆሮ ያለህ!

ተካልኝ ነጋ (ዶ/ር) በዚህ ጽሑፉ፣ ‘አድማጭ መሆን ለምን ተሳነን? ለምን ተናጋሪ ብቻ ሆንን? በማድመጥ ውስጥ እናገኝ የነበረውን ኁልቁ መሳፍርት በረከትኣ ለምን እናጣለን?’ ሲል አንባቢን ይሞግታል።

ለዋጭ ለውጦች!

አድማጭ የሚሹ ብዙ ጩኸቶች እዚህም እዚያም አሉ። የሰው ልጅ የስኬት ብቻ ሕይወት የለውም፤ ውድቀትም አንዱ የኑሮ ገጽታ ነው። በውድቀት ውስጥ ብዙ ሕመሞች በሰዎች ልብ ውስጥ ተቀርቅረው ይገኛሉ። እነዚህ ሕመሞች እንዲታከሙ የሚያስችሉ አድማጭ ጆሮ ያላቸው መካሪዎች በእጅጉ ያስፈልጉናል ይላል ይህ የተካልኝ ነጋ (ዶ/ር) ጽሑፍ።

አቋራጭ ስሌቶች

“ለጥልቅ አሳቢያን ዐሥርት ዓመታት የወሰዱ ጉዳዮችን፣ በአንድ ቀን የቁም አሰላስሎ ወይም በአንድ ሰው የመጽሐፍ መግቢያ ንባብ የምንደመድም የአቋራጭ መንገድ አፍቃሪያን አለን።” ተካልኝ ነጋ (ዶ/ር)

የመተማመን ድልድዩን እንጠግን

ይቅርታ መጠየቅ ምን ማለት ነው? ሰዎች ይቅርታ ለመጠየቅ ለምን ይቸገራሉ? የተሠራው በደል በተበዳዩ ላይ ካሳድረው ጉዳት አንጻር፣ የበዳዩ ይቅርታ ጥየቃ የሚያጎናጸፈው ሥነ ልቦናዊ ፋይዳ ምንድን ነው?

ያላለቀው ጉዞ!

ተካልኝ ነጋ (ዶ/ር) “ያላለቀው ጉዞ!” ሲል በሰየመው ጽሑፉ፣ በልማትና ዕድገት መካከል ያለውን መሠረታዊ ልዩነት በማስቃኘት፣ አገራችን ኢትዮጵያ “ሄድ መጣ” እያለ የሚያማልላትን ተስፋ በሙሉ እጇ ትጨብጠው ዘንድ ልታደርጋቸው የሚገቡ ያላቸውን አንዳንድ ነጥቦች እንደሚከተለው ያስነብባል።

ዛሬ ያልተመቸን ሕዝቦች

ኢትዮጵያውያን በቀድሞው ዘመን ናፋቂነት የዛሬውን ዕድል እያባከንን እንደ ሆነ፣ ተካልኝ ነጋ (ፒ.ኤች.ዲ) በዚህ መጣጥፉ ይሞግታል። በተለይም በትላንት ናፍቆት ውስጥ ስለ “ጀግኖቻችን” ያለን ምልከታ፣ የዛሬውን አብሮ ነዋሪ ወንድማችንን እንዳይጎዳውም ያሳስበናል።

የሰሞኑ የኅብረቱ ትጭጭት (ጋብቻ)

የአብያተ ክርስቲያናት ኅብረት ቁጥራቸው 150 የሚደርሱ “መንፈሳዊ” ተቋማትን በአጋር አባልነት የመቀበሉን መራር እውነታ አውቀናል። በኅብረቱ መግለጫ ሚዲያ ተጠርቶላቸው የካሜራ ክብር ያገኙት ግን አራቱ ብቻ ናቸው። ሌሎቹ ነገራቸው በድብስብስ የታለፈ ሊባል የሚችል ነው። ራሳቸው በማኅበራዊ ሚዲያ ብቅ ብለው እኛም ነበርንበት ባይሉ መኖራቸውን ከቶውን ባላወቅን ነበር። አራቱ ትኩረት ያገኙበት ምክንያት፣ በተክለ ሰውነት “አውራዎች” ስለሆኑ ይሆናል።

ምስክርነቶቻችን ቢፈተሹሳ?

“ሀገሩን ሁሉ በትምህርቱ የሚያስደምም ሰው ራስ ሆቴል አከባቢ ተነስቷል!” የሚል የወዳጆቼ ጉትጎቷ ቀን ከሌት ቢከታተለኝ፣ በአንድ በኩል በርካቶችን ያስደመመውን ትምህርት ለመቋደስ ብሎም ከዚሁ ከአመለጠህ የወዳጆቼ ጉትጎታ ለማምለጥ በሚል ሁለት ልብ ነበር እግሮቼን ያቀናሁት። በእርግጥም በዛች ቀን ብቻ ወዳጆቼን ምን ነካብኝ ያሰኙ አስተምሮቶችን በአይኔ በብረቱ ተመልክቼ ተመልሻለው፤ ዳግም አልተመለስኩም፤ ደግሞም አልመለስም።

የቃላት ጡጫ እና ጉዳቱ

የብእር ሐሳብ ከማይነጥፍባቸው ነገሮች አንዱ የፍቅር ጉዳይ ነውና ዛሬም ስለ ፍቅር እናውጋ። የፍቅር ታሪኮችን ስናደምጥ ደግሞ ተያያዥ ስሜት መውረሩ አይቀርም። አንዳንዱ ታሪክ ልባችንን ጮቤ የሚያስረግጥ ነው፤ የተከፈለው መሥዋዕትነት ‘ብዙ ውኾች’ ፍቅርን ለማጥፋት የፈረጠመ ጡጫ እንደሌላቸው ምስክር ነው (መኀ. 8፥7)። ሌላው ደግሞ ውስጣችን በቁጭት እንዲብሰከሰክ ምክንያት የሚሆን ነው (2 ሳሙ. 13፥1-20)። በስመ ፍቅር አንዳንዶች የተጎነጩትን ጭቆና እና ግፍን ተመልክቶ አለመቆጣት በርግጥም የተባባሪ ያህል ያስቆጥራል።

የኋለኛው ዘመን አሻራ በፍቅር ፍኖት ላይ

የስሜትና የሐሳብ ቁርኝት የፍቅር አካላት ሆነው ይነሣሉ። ያልተነጣጠለ አብሮነታቸውም አንደኛው ከሌለ የሌላው ሕልውና ጥያቄ ውስጥ እንዲወድቅ ያደርጋል። ለነገሩ፣ ፍቅርን ከተያያዥ ስሜትና ሐሳብ አፋቶ ትርጉም ባለው መልኩ ማሰብስ ማን ይችላል? ተፈቃሪን በምናብ አጣምሮ ራስን ማብገንን ሆነ የመጨረሻዋ ተጠባቂ ሰከንድ አምልጣን ዘላለምን የተቀላቀለች ይመስል በቁንጥንጥ “ውዳችንን” መጠበቃችን በምንስ ይብራራል? በእርግጥም ከፍቅር ጋር ተያይዞ የምናሳየው መሰጠት፣ ሐዘኔታ፣ ቅናት፣ መረበሽ ከስሜትና ከሐሳብ ትሥሥር ጋር ይዛመዳሉ። የስሜቶቻችን እና የሐሳቦቻችን ቁርኝት ከሌሎች ተደምሮ ባዕድነትን ገፎ ተፈቃሪያችን በአንድት የሚገምድ ምስጢር ነው (ዘፍ. 2፥23-24)።

ፍቅርን የመግለጫ መንገዶች

በፍቅር የተጋመዱ ጥንዶች ትሥሥራቸውን አስመልክቶ ጥያቄዎችን ማንሣታቸው አይቀርም። አንዳንዱ ጥያቄ የሚሰነዘረው ለአፍቃሪው ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ መልስ ከተፈቃሪው ይሻል። ከሚነሡት ጥያቄዎች መካከል አንደኛው “የፍቅር ጥያቄ” ነው። ራሳችንን፣ “በርግጥ አፈቅራታለሁኝ?”፣ “እሷስ ከልቧ ታፈቅረኛለች?” እንላለን። መነሾው ቢለያይም፣ በደስታ መኻል ስንቅር የሚል ጥያቄ እንደ መሆኑ ያስጠላል፤ ያስፈራልም። ሲ. ኤስ. ሊዊስም፣ “ፍቅር በሕይወታችን ካለ ጽኑና ቀጣይ ደስታ ከዐሥሩ የዘጠኙን እጅ ድርሻ ይወስዳል” እንደ ማለቱ ጥያቄው አይናቅም።

ፍቅር ማለምለሚያ

በፍቅር የተጋመዱ ጥንዶች ትሥሥራቸውን አስመልክቶ ጥያቄዎችን ማንሣታቸው አይቀርም። አንዳንዱ ጥያቄ የሚሰነዘረው ለአፍቃሪው ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ መልስ ከተፈቃሪው ይሻል። ከሚነሡት ጥያቄዎች መካከል አንደኛው “የፍቅር ጥያቄ” ነው። ራሳችንን፣ “በርግጥ አፈቅራታለሁ?”፣ “እሷስ ከልቧ ታፈቅረኛለች?” እንላለን። መነሾው ቢለያይም፣ በደስታ መኻል ስንቅር የሚል ጥያቄ እንደ መሆኑ ያስጠላል፤ ያስፈራልም። ሲ. ኤስ. ሊዊስም፣ “ፍቅር በሕይወታችን ካለ ጽኑና ቀጣይ ደስታ ከዐሥሩ የዘጠኙን እጅ ድርሻ ይወስዳል” እንደ ማለቱ ጥያቄው አይናቅም።

የማንን ጥያቄ ልጠይቅ? – Semayawi Thought

በርካቶች ይጠይቃሉ፤ የጥያቄያቸውም መዳረሻ ግን ራሳቸው አይደሉም፡፡ ጉጉታቸውም ሆነ ኳተናቸው ሸልቅቆ መመልከት የሚፈልገው የሌላን ሰው ህይወት ነው፡፡ እንዲያ አይነቱ ፍላጎት በልጓም ተገቶ፣ ከምንም በፊት የራሱን መንገድ እንዲጠበጥብ ሊደረ…

የልጆቾ ወላጅ ማነው? – Semayawi Thought

ርእሴን ያነበበ ሰው፣ “ወዴት ወዴት ነው?” ሊል ይችላል ፡፡ ቀዩኝ! ወዴትም አይደለም፡፡ አሊያም፣ “ስያሜው ራሱ የሚጋጭ ነው፤” በሚል በሰላ ሂስ መጣጥፌን ሊጀመርው ይመርጥም ይሆናል ፡፡ ግድ የለም ጥቂት ታግሳችሁ ስሙኝ፡፡ በአካል ወላጆ…

‹‹ባልንጀራዬ›› ይሰኛል፤ በማኅበራዊ ድረገጽ ፌስቡክ ‹‹ባልንጀራዬ /Balinjeraye›› በሚል ሥያሜ ይገኛል። ሌላውን እንደራስ የመውደድ እንቅስቃሴ ነው። በአሜሪካዊው አንድሪው ዴኮርት (ዶ/ር) የተመሠረተ እንቅስቃሴ ሲሆን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ፋካሊቲ የአካውንቲንግ እና ፋይናንስ ረዳት ፕሮፌሰር ተካልኝ ነጋ ምሥረታው ላይ አሉበት። ሰላምና

Go to Top